የተማረ ትውልድን ማፍራት አገርን ማዳን ነው !!
በበጎ ፈቃደኝነት ተነሳሺነት ፣ በፈረንሳይ ኗሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያኖችና በፈረንሳይ ተወላጅ ጓደኛሞች መካከል በኢትዮጵያ ውስጥ በችግር ላይ ወድቀው ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎችና ት/ቤቶች ፣ ያለባቸውን ችግር አብረዋቸው ለመካፈል ፣ የፈረንሳይ 1901 ዓ/ም ሕግ በሚፈቅደው መሠረት በአውሮፓውያን ቀን አቆጣጠር በ ሐምሌ 18 – 1996 ዓ/ም « Association Bourgeons » ፣ ሲነበብ ‘’ቡርዦ’’ ሲተረጎም ደግሞ ‘’ እንቡጥ’’ በሚለው ስም ማኅበሩ ተሰይሞ ተቋቋመ :: በዚህ ሕግ አንቀጽ 1901 ስር የሚተዳደሩ ማኅበሮች ምንም የመተዳደሪያ ገቢ የሌላቸው ወይም በንግድ ዓለም ተሰማርተው አትራፊ ያልሆኑ ግብረሰናይ ማኅበሮች ናቸው ::
ስለዚህ እንቡጥ ወይም Bourgeons በዚህ ሕግ ስር የሚተዳደር በመሆኑ ፣ በመዋቅሩ ደረጃ ፣ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ወይም (NGO / Non-Governmental Organization) ያልሆነ በመሆኑ ፣ ከሌላ የውጭ ድርጅት ምንም ዓይነት ገቢ የሌለው ሲሆን ፣ የገንዘብ መዋጮ ፣ የጉልበት ፣ የዕውቀት ና የነጻ አገልግሎት ፣ ከበጎ አድራጊ አባሎቹ በሚሰጠው ልገሳ የሚተዳደር ፣ በበጎ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ የወንድማማቾች ማኅበር ነው ::


የኛ ተልዕኮ
መንባት፣ መጻፍ፣ መቁጠር እና በተቻለ መጠን ተጨማሪ መማር። የ »ቡርጆን » አላማ ይህ ነው!
እንዴት መርዳት እንደሚቻል
01.
ልጅን ስፖንሰር ያድርጉ
ቀጥተኛ የትምህርት ድጋፍ ያቅርቡ

02.
ልገሱ
ፈንድ ስኮላርሺፕ እና ፕሮግራሞች

03.
አባል ይሁኑ
ደጋፊ ማህበረሰባችንን ይቀላቀሉ

የእኛ ልዩ አቀራረብ
ቀጥተኛ ድጋፍ
እያንዳንዱ ልገሳ ለተቸገሩ ልጆች በቀጥታ ግልጽ በሆነ አጋርነት መድረሱን እናረጋግጣለን።
አጠቃላይ ግልጽነት
እያንዳንዱ ዩሮ በሃላፊነት እና በብቃት ለህጻናት ትምህርት ጥቅም ላይ መዋሉን በማረጋገጥ ተግባራችን በኢትዮጵያ በተመረጡ ባለስልጣናት እና የአካባቢ መሪዎች ቁጥጥር ስር ነው።
የሰው ግንኙነት
የማህበሩ አባላት ከትምህርት ቤቱ እና ከልጆች ጋር የመተማመን ግንኙነትን ለመጠበቅ እና ስለእድገታቸው ተጨባጭ ዜና ለማምጣት በየጊዜው ወደ ኢትዮጵያ ይጓዛሉ።
