በበጎ ፈቃደኝነት ተነሳሺነት ፣ በፈረንሳይ ኗሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያኖችና በፈረንሳይ ተወላጅ ጓደኛሞች መካከል በኢትዮጵያ ውስጥ በችግር ላይ ወድቀው ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎችና ት/ቤቶች ፣ ያለባቸውን ችግር አብረዋቸው ለመካፈል ፣ የፈረንሳይ 1901 ዓ/ም ሕግ በሚፈቅደው መሠረት በአውሮፓውያን ቀን አቆጣጠር በ ሐምሌ 18 - 1996 ዓ/ም « Association Bourgeons » ፣ ሲነበብ ‘’ቡርዦ’’ ሲተረጎም ደግሞ ‘’ እንቡጥ’’ በሚለው ስም ማኅበሩ ተሰይሞ ተቋቋመ :: በዚህ ሕግ አንቀጽ 1901 ስር የሚተዳደሩ ማኅበሮች ምንም የመተዳደሪያ ገቢ የሌላቸው ወይም በንግድ ዓለም ተሰማርተው አትራፊ ያልሆኑ  ግብረሰናይ ማኅበሮች ናቸው ::
ስለዚህ እንቡጥ ወይም Bourgeons በዚህ ሕግ ስር የሚተዳደር በመሆኑ ፣ በመዋቅሩ ደረጃ ፣ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ወይም (NGO / Non-Governmental Organization) ያልሆነ በመሆኑ ፣ ከሌላ የውጭ ድርጅት ምንም ዓይነት ገቢ የሌለው ሲሆን ፣ የገንዘብ መዋጮ ፣ የጉልበት ፣ የዕውቀት ና የነጻ አገልግሎት ፣ ከበጎ አድራጊ አባሎቹ በሚሰጠው ልገሳ የሚተዳደር ፣ በበጎ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ የወንድማማቾች ማኅበር  ነው ::

እስካሁን ያለው አሃዝ እንደሚያመለክተው ፣ የእንቡጥ (Bourgeons) ማኅበር ከተመሠረተ 29 አመት ግዜ ጀምሮ የተከታተልናቸው ተማሪዎች ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ዩኒቨርሲቲ ፣ በአስተማሪነት ፣ በሰዓሊነት ፣ በመኪና ሜካኒክ ፣ በፀጉር ስራ ፣ በጋራዥ ፣ በኮንፒተር ፣ በሂሳብ አያያዝ ፣ በባንክ ሥራ ፣ በፀሐፊነት በንግድ አለም ወዘተ በተለያየ የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ወደ 400 ተማሪዎች ራሳቸውን ችለው በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ሙሉ ተሳታፊ ለመሆን በቅተዋል ። ይኽ እንግዲህ ከ8ኛ እስከ 12ኛ ተምረው ራሴን በሚመስለኝ መንገድ ልምራ ብለው ትምህርታቸውን አቋርጠው በተለያየ የስራ አለም ውስጥ የተሰማሩትን በሺ የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ሳይጨምር ነው ።

ለቁም ነገር በደረሱ ሰአት ፣ የሚጽፉት የስንብት ደብዳቤ ባጭሩ ሲነበብ :- « ለዚህ ወግ ስላበቃችሁኝ እያመሰገንኩ ከቻላችሁ በኔ ቦታ ሌላ ወጣት ውሰዱ ። እኔ ደግሞ አቅሜ ከፈቀደ በወጣቶች ክለብ ውስጥ በመሳተፍ ሌሎቹን ለመርዳት ቃል እገባለሁ » ይላል ።

መጀመሪያ ከነበሩት ውስጥ አግብተው ልጆች ያፈሩ ጥቂት አይደሉም ፣ እስካሁንም ከማኅበሩ ጋር የሰላምታ ግንኙነታቸውን አላቋረጡም ። ድንቅዬዎቻችን ናቸው ::
ስለዚህ ፣ በእንቡጥ ማኅበር ጥላ ሥር ሆነው ለሚማሩ ተማሪዎች ፣ የተጀመረላቸው ዕርዳታ በችግር ምክንያት የመቋረጥ እድል እንዳይገጥመው የድርሻዎትን ያበርክቱላቸው ፣ ላልሰሙ አሰሙ !!

ጥያቄያቸው ምንድነው ?
የዓመት ፣ የት/ቤት መመዝገብያ ክፍያ ፣ የደንብ ልብስ ፣ መጽሐፍ ፣ ደብተር ፣ እርሳስ ፣ አጠቃላይ የዓመት ትምህርት ቁሳቁስ መግዣ ወዘተ የመሳሰሉት ናቸው ::
ይኽ ከተሟላላቸው የት/ቤት በርን በችግር ምክንያት ከማንኳኳት ዳኑ ማለት ነው ::
---

በተማሪዎቻችን ስም ሆነን ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ልባዊ ምስጋና እናቀርባለን ።
ከእንቡጥ ማኅበር ቢሮ  

 


ፈረንሳይ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታላቅ ርዳታ 400 ኪ/ግ የሚመዝን መድኃኒትና ተሽከርካሪ ወንበር ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች እንዲሁም ዐድዋ በር ት/ቤት ላሉት ተማሪዎች ትምህርት ሰጭ ዕቃዎችን ይዘው በተግባር ለማዋል የእንቡጥ (Bourgeons ) ማኅበርን ወክለው ወ/ሮ ካሚይ (መላኳ) ና አቶ ደጀን ይርጉ በጥቅምት ወር 2022 ዓ/ም ላይ ወደ ኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉዞ የሚያመለክት በምስልና ቪድዎ የተደገፈ ይመልከቱ ።
https://photos.app.goo.gl/75tJ7YS4RuycRPFu8

በዚሁ ወቅት ወ/ሮ ካሚይ (መላኳ) ና አቶ ደጀን ይርጉ የእንቡጥ ማኅበርን በወከል በዐድዋ በር ት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ከት/ቤቱ ኃላፊዎች ፣ ሰራተኞች ፣ የተማሪ ወላጆች ፣ ተማሪዎች ፣ እንዲሁም ከእንቡጥ (Bourgeons ) ወጣቶች መረዳጃ ማኅበር ጋር የነበረውን ግኑኝነት የሚያሳይ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ ወገን ለወገን በሚል በሚደረገው የመረዳዳት ዘመቻ ዙርያ የኢትዮጵያ ARTS TV ያቀነባበረውን የ2ት ዙር የፊልም ቀረጻ ይመልከቱ ።

ARTS TV N°1
https://youtu.be/36P6r5Onffs

ARTS TV N°2
https://youtu.be/gQwUMKvEzso

በእንቡጥ ማኅበር ጥላ ስር ሆነው የሚማሩ የ2014 (2022) ዓ/ም ተማሪዎች አልበም ፎቶ

የተማረ ትውልድን ማፍራት አገርን ማዳን ነው !!

የሚጽፍ የሚያነብ የሚያሰላ ትውልድ ይመራመራል ፣
ለምን የሚለውንም ግንዛቤ ያገኛል ።
ከዚኽም አልፎ ቤተሰብና አገርን ይመራል ።

ስለዚህ ፣ ይኽን ዕድል እንስጣቸው !!

ከ400 ተማሪዎች ውስጥ የእንቡጥ ማኅበር በትምህርት አሳድጎ ለቁም ነገር ካበቃቸው ወጣቶች አንዱ ዘመኔው ይማኖ ሲሆን ፣ በአሁን ግዜ በመንግስት ት/ቤት የሂሳብ መምህር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል ። የሁላችንም ምሳሌ ስለሆነ ተግባሩን በቪድዮ ይመልከ

በአድዋ በር ት/ቤት የእንቡጥ ማኅበር 20ኛ የልደት ክብር ቀን በሙዚቃ መምህሩና የወጣቶች ክለብ ኃላፊ በሆነው ዘላለም እንድርያስ የተዘመረ

የእንቡጥ ማኅበር ሕይወት በቪዲዮና በራዲዮ ቃለ ምልልስ ዙርያ

የዓድዋ በር ት/ቤት የነበረው ገጽታ በፊትና በኋላ ከእንቡጥ ማኅበር ጋር የመጀመርያው ትውውቅ በቪድዮ 1994-1998 ዓ/ም

_____________________________________________________________________________

አጋር የእንቡጥ ማኅበር የኢትዮጵያ ምግብ ቤቶች ድረገጽ

ፓሪስ
:
ጎጆምኒሊክአቢሲኒያ ካፌኢትዮጵያ ሐበሻእንጦጦለንጉስ ለላክ ጣና አጼ ቴዎድሮስአዲስ አበባሌሳቨር ደአቢሲኒእቴጌ ጣይቱ ኢትዮ-ሳሪስ ... ስዊዝ : አቢሲኒያ-ሎዛንአቢሲኒያ-ሲኦአቢሲኒያ ነሻቴልአቢሲኒያ-በርን አቢሲኒያ-ፍሪቡር ---- አሜሪካ - ዳላስ : ቡክሪ ካተሪንግ

_____________________________________________________________________________

የእንቡጥ ማኅበር አድራሻ - Association BOURGEONS 27 André Tessier 94120 France | | የማኅበሩን ዓላማ ለሌላው በማስተዋወቅ እንርዳ ||የእድሳት ቀን የካቲት ፲፮ ፳፻፲፭ ዓ/ም

_____________________________________________________________________________