እስካሁን ያለው አሃዝ እንደሚያመለክተው ፣ የእንቡጥ (Bourgeons) ማኅበር ከተመሠረተ 29 አመት ግዜ ጀምሮ የተከታተልናቸው ተማሪዎች ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ዩኒቨርሲቲ ፣ በአስተማሪነት ፣ በሰዓሊነት ፣ በመኪና ሜካኒክ ፣ በፀጉር ስራ ፣ በጋራዥ ፣ በኮንፒተር ፣ በሂሳብ አያያዝ ፣ በባንክ ሥራ ፣ በፀሐፊነት በንግድ አለም ወዘተ በተለያየ የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ወደ 400 ተማሪዎች ራሳቸውን ችለው በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ሙሉ ተሳታፊ ለመሆን በቅተዋል ። ይኽ እንግዲህ ከ8ኛ እስከ 12ኛ ተምረው ራሴን በሚመስለኝ መንገድ ልምራ ብለው ትምህርታቸውን አቋርጠው በተለያየ የስራ አለም ውስጥ የተሰማሩትን በሺ የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ሳይጨምር ነው ።
ለቁም ነገር በደረሱ ሰአት ፣ የሚጽፉት የስንብት ደብዳቤ ባጭሩ ሲነበብ :- « ለዚህ ወግ ስላበቃችሁኝ እያመሰገንኩ ከቻላችሁ በኔ ቦታ ሌላ ወጣት ውሰዱ ። እኔ ደግሞ አቅሜ ከፈቀደ በወጣቶች ክለብ ውስጥ በመሳተፍ ሌሎቹን ለመርዳት ቃል እገባለሁ » ይላል ።
መጀመሪያ ከነበሩት ውስጥ አግብተው ልጆች ያፈሩ ጥቂት አይደሉም ፣ እስካሁንም ከማኅበሩ ጋር የሰላምታ ግንኙነታቸውን አላቋረጡም ። ድንቅዬዎቻችን ናቸው ::
ስለዚህ ፣ በእንቡጥ ማኅበር ጥላ ሥር ሆነው ለሚማሩ ተማሪዎች ፣ የተጀመረላቸው ዕርዳታ በችግር ምክንያት የመቋረጥ እድል እንዳይገጥመው የድርሻዎትን ያበርክቱላቸው ፣ ላልሰሙ አሰሙ !!
ጥያቄያቸው ምንድነው ?
የዓመት ፣ የት/ቤት መመዝገብያ ክፍያ ፣ የደንብ ልብስ ፣ መጽሐፍ ፣ ደብተር ፣ እርሳስ ፣ አጠቃላይ የዓመት ትምህርት ቁሳቁስ መግዣ ወዘተ የመሳሰሉት ናቸው ::
ይኽ ከተሟላላቸው የት/ቤት በርን በችግር ምክንያት ከማንኳኳት ዳኑ ማለት ነው ::
---
በተማሪዎቻችን ስም ሆነን ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ልባዊ ምስጋና እናቀርባለን ።
ከእንቡጥ ማኅበር ቢሮ |
|
ፈረንሳይ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታላቅ ርዳታ 400 ኪ/ግ የሚመዝን መድኃኒትና ተሽከርካሪ ወንበር ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች እንዲሁም ዐድዋ በር ት/ቤት ላሉት ተማሪዎች ትምህርት ሰጭ ዕቃዎችን ይዘው በተግባር ለማዋል የእንቡጥ (Bourgeons ) ማኅበርን ወክለው ወ/ሮ ካሚይ (መላኳ) ና አቶ ደጀን ይርጉ በጥቅምት ወር 2022 ዓ/ም ላይ ወደ ኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉዞ የሚያመለክት በምስልና ቪድዎ የተደገፈ ይመልከቱ ።
https://photos.app.goo.gl/75tJ7YS4RuycRPFu8
በዚሁ ወቅት ወ/ሮ ካሚይ (መላኳ) ና አቶ ደጀን ይርጉ የእንቡጥ ማኅበርን በወከል በዐድዋ በር ት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ከት/ቤቱ ኃላፊዎች ፣ ሰራተኞች ፣ የተማሪ ወላጆች ፣ ተማሪዎች ፣ እንዲሁም ከእንቡጥ (Bourgeons ) ወጣቶች መረዳጃ ማኅበር ጋር የነበረውን ግኑኝነት የሚያሳይ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ ወገን ለወገን በሚል በሚደረገው የመረዳዳት ዘመቻ ዙርያ የኢትዮጵያ ARTS TV ያቀነባበረውን የ2ት ዙር የፊልም ቀረጻ ይመልከቱ ።
ARTS TV N°1
https://youtu.be/36P6r5Onffs
ARTS TV N°2
https://youtu.be/gQwUMKvEzso
በእንቡጥ ማኅበር ጥላ ስር ሆነው የሚማሩ የ2014 (2022) ዓ/ም ተማሪዎች አልበም ፎቶ
የተማረ ትውልድን ማፍራት አገርን ማዳን ነው !!
የሚጽፍ የሚያነብ የሚያሰላ ትውልድ ይመራመራል ፣
ለምን የሚለውንም ግንዛቤ ያገኛል ።
ከዚኽም አልፎ ቤተሰብና አገርን ይመራል ።
ስለዚህ ፣ ይኽን ዕድል እንስጣቸው !!
ከ400 ተማሪዎች ውስጥ የእንቡጥ ማኅበር በትምህርት አሳድጎ ለቁም ነገር ካበቃቸው ወጣቶች አንዱ ዘመኔው ይማኖ ሲሆን ፣ በአሁን ግዜ በመንግስት ት/ቤት የሂሳብ መምህር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል ። የሁላችንም ምሳሌ ስለሆነ ተግባሩን በቪድዮ ይመልከቱ
በአድዋ በር ት/ቤት የእንቡጥ ማኅበር 20ኛ የልደት ክብር ቀን በሙዚቃ መምህሩና የወጣቶች ክለብ ኃላፊ በሆነው ዘላለም እንድርያስ የተዘመረ |
የእንቡጥ ማኅበር ሕይወት በቪዲዮና በራዲዮ ቃለ ምልልስ ዙርያ
የዓድዋ በር ት/ቤት የነበረው ገጽታ በፊትና በኋላ ከእንቡጥ ማኅበር ጋር የመጀመርያው ትውውቅ በቪድዮ 1994-1998 ዓ/ም
|